ሀገር አቀፉ የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ተጀመረ።
የ2017 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ (12ኛ ክፍል) ፈተና በዛሬው ዕለት ተጀምሯል።
የመጀመሪያ ዙር የተፈጥሮ ሳይንስ ፈተና በሁሉም የመፈተኛ ጣቢያዎች መሰጠት ተጀምሯል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ፣ የሚኒስቴሩ አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታ ፕሮፌሰር ክንደያ ገ/ህይወት እንዲሁም የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር ኢ/ር ነጋሽ ዋጌሾ በቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ተገኝተው ፈተናውን አስጀምረዋል።
ዘንድሮ በወረቀትና በበየነ መረብ ከ608 ሺ በላይ ተማሪዎች ፈተናቸውን ይወስዳሉ ተብሎ ይጠበቃል።
መረጃው የትምህርት ሚኒስቴር ነው።
©️ tikvahethiopia
|| @ASTU_Network
የ2017 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ (12ኛ ክፍል) ፈተና በዛሬው ዕለት ተጀምሯል።
የመጀመሪያ ዙር የተፈጥሮ ሳይንስ ፈተና በሁሉም የመፈተኛ ጣቢያዎች መሰጠት ተጀምሯል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ፣ የሚኒስቴሩ አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታ ፕሮፌሰር ክንደያ ገ/ህይወት እንዲሁም የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር ኢ/ር ነጋሽ ዋጌሾ በቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ተገኝተው ፈተናውን አስጀምረዋል።
ዘንድሮ በወረቀትና በበየነ መረብ ከ608 ሺ በላይ ተማሪዎች ፈተናቸውን ይወስዳሉ ተብሎ ይጠበቃል።
መረጃው የትምህርት ሚኒስቴር ነው።
©️ tikvahethiopia
|| @ASTU_Network
❤5🕊5
#NationalExam🇪🇹
ፆታዊ ትንኮሳ የፈፀሙ ሦስት ተማሪዎች ከሀገር አቀፍ ፈተና ታገዱ።
በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተሰጠ ባለው የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ለመፈተን ወደ መቱ ዩንቨርስቲ ከገቡት ተማሪዎች ውስጥ ሦስት ተማሪዎች በሴት ተማሪዎች ላይ ዕፆታዊ ትንኮሳ በመፈፀማቸው ከፈተናው መታገዳቸውን የመቱ ዩንቨርስቲ አስታወቀ።
ዩኒቨርስቲው ፕሬዚዳንት አለሙ ድሳሳ (ዶ/ር) ለቲክቫህ ኢትዮጵያ " በርካታ ተማሪዎች ወደ ግቢ ከገቡ በኃላ ወጣ ያለ ፀባይ እያሳዩ ነበር " ብለዋል።
ዩኒቨርስቲውም ለፈተናው ከተቋቋመ ኮማንድፖስት ጋር በመሆን የመቆጣጠር ሥራ ሲሰራ እንደነበር በማንሳት፤ ሦስቱ ተማሪዎች በሴት ተማሪዎች ላይ ሰኔ 22 ቀን 2017 ዓ.ም አደባባይ ላይ ትንኮሳ መፈፀማቸውን ተበድለናል ብለው በመጡ ሴቶች ቅሬታ እና ዩንቨርስቲውም ባደረገው ማጣራትብ ድርጊቱን መፈፀማቸውን አረጋግጧል።
" ትንኮሳ አድራጊዎቹ በአደባባይ ሴቶችን በግድ መሳም፤ ልብሳቸውን መገለብ እና መንካት የማይፈቀድ የአካላቸውን ክፍል በመንካታቸው ሴቶቹ ባቀረቡት አቤቱታ መሰረት ህጋዊ እርምጃ ተወስዶባቸዋል " ብለዋል።
በዚህ የተነሳ የትንኮሳ ወንጀል በፈፀሙ ወንዶች ላይ ከዘንድሮው አመት ፈተና እንዲታገዱ መደረጉን ገልጸዋል።
ተማሪዎቹ አንዱ ከኢሉ አባቦር ዞን በቾ ወረዳ ሁለቱ ደግሞ ከምስራቅ ወለጋ የመጡ መሆናቸውን ፕረዝዳንቱ አክለዋል።
እርምጃ ከተወሰደ በኃላ በግቢው ሲስተዋል የነበረው የተማሪዎች ሥነ ምግባር መሻሻሉንም ተናግረዋል።
ወደፊትን ተመሳሳይ ችግሮች እንዳይፈጠር ትምህርት ቤቶች የፈተና ሥነ ምግባር ላይ ለተማሪዎች ግንዛቤ መስጠት እንዳለባቸው የገለፁት አለሙ ድሳሳ (ዶ/ር) ሴት ተማሪዎችም ራሳቸውን እንዲጠብቁና ለትንኮሳ ራሳቸውን እንዳይጋብዙም ጠይቀዋል።
©️ tikvahethiopia
|| @ASTU_Network
ፆታዊ ትንኮሳ የፈፀሙ ሦስት ተማሪዎች ከሀገር አቀፍ ፈተና ታገዱ።
በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተሰጠ ባለው የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ለመፈተን ወደ መቱ ዩንቨርስቲ ከገቡት ተማሪዎች ውስጥ ሦስት ተማሪዎች በሴት ተማሪዎች ላይ ዕፆታዊ ትንኮሳ በመፈፀማቸው ከፈተናው መታገዳቸውን የመቱ ዩንቨርስቲ አስታወቀ።
ዩኒቨርስቲው ፕሬዚዳንት አለሙ ድሳሳ (ዶ/ር) ለቲክቫህ ኢትዮጵያ " በርካታ ተማሪዎች ወደ ግቢ ከገቡ በኃላ ወጣ ያለ ፀባይ እያሳዩ ነበር " ብለዋል።
ዩኒቨርስቲውም ለፈተናው ከተቋቋመ ኮማንድፖስት ጋር በመሆን የመቆጣጠር ሥራ ሲሰራ እንደነበር በማንሳት፤ ሦስቱ ተማሪዎች በሴት ተማሪዎች ላይ ሰኔ 22 ቀን 2017 ዓ.ም አደባባይ ላይ ትንኮሳ መፈፀማቸውን ተበድለናል ብለው በመጡ ሴቶች ቅሬታ እና ዩንቨርስቲውም ባደረገው ማጣራትብ ድርጊቱን መፈፀማቸውን አረጋግጧል።
" ትንኮሳ አድራጊዎቹ በአደባባይ ሴቶችን በግድ መሳም፤ ልብሳቸውን መገለብ እና መንካት የማይፈቀድ የአካላቸውን ክፍል በመንካታቸው ሴቶቹ ባቀረቡት አቤቱታ መሰረት ህጋዊ እርምጃ ተወስዶባቸዋል " ብለዋል።
በዚህ የተነሳ የትንኮሳ ወንጀል በፈፀሙ ወንዶች ላይ ከዘንድሮው አመት ፈተና እንዲታገዱ መደረጉን ገልጸዋል።
ተማሪዎቹ አንዱ ከኢሉ አባቦር ዞን በቾ ወረዳ ሁለቱ ደግሞ ከምስራቅ ወለጋ የመጡ መሆናቸውን ፕረዝዳንቱ አክለዋል።
እርምጃ ከተወሰደ በኃላ በግቢው ሲስተዋል የነበረው የተማሪዎች ሥነ ምግባር መሻሻሉንም ተናግረዋል።
ወደፊትን ተመሳሳይ ችግሮች እንዳይፈጠር ትምህርት ቤቶች የፈተና ሥነ ምግባር ላይ ለተማሪዎች ግንዛቤ መስጠት እንዳለባቸው የገለፁት አለሙ ድሳሳ (ዶ/ር) ሴት ተማሪዎችም ራሳቸውን እንዲጠብቁና ለትንኮሳ ራሳቸውን እንዳይጋብዙም ጠይቀዋል።
©️ tikvahethiopia
|| @ASTU_Network
❤8😁4
የ85 ዓመቱ አባት የአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲን መንገድ ያዙ!
የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ለመውሰድ ወደ አርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ ጉዞ የጀመሩት አቶ ማኖ ማገሶ የዘንድሮውን ፈተና ከምን ጊዜውም በተለየ መልኩ ታሪካዊ አድርገውታል።
የ85 ዓመቱ አባት የካቻ ካሻሶ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪ ሲሆኑ፣ በዚህ ዕድሜያቸው ፈተና መፈተናቸው በእርግጥም ትልቅ አርአያነት ነው።
አቶ ማኖ ማገሶ
* የአምስት ወንዶችና
* የስድስት ሴቶች፣ በድምሩ የአስራ አንድ ልጆች አባት ናቸው።
ቀደም ሲል በጋሞ ጎፋ ክፍለ ሀገር ጋርዱላ አውራጃ የገበሬ ማኅበር ጽ/ቤት ኃላፊ ሆነው ሰርተዋል።
ከዚህም በላይ በገረሴ ወረዳ ጌዣ ደንን በማስተካከል የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርን ከጀመሩት መካከል አንዱ ናቸው።
የካሻሶ ትምህርት ቤትን በማቋቋም እና ለመምህራንና ለአካባቢው ህብረተሰብ ምቹ እንዲሆን ማኖ ገበያን (ወይም ካሻሶ ገበያን) በመክፈት ትልቅ አስተዋጽኦ አድርገዋል።
ልጆቻቸውን በማስተማርም አርባ ምንጭ፣ አዲስ አበባ አልፎ ተርፎም ቻይና ድረስ በትምህርት እንዲደርሱ የረዱ ታላቅ አባት ናቸው።
የቦንኬ ወረዳ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት እንዳስታወቀው፣ የአቶ ማኖ ማገሶ ለ2017 ዓ.ም ሁለተኛ ዙር ማህበራዊ ሳይንስ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተና መፈተን እጅግ ልዩና ታሪካዊ ክስተት ነው።
መልካም ዕድል ለአቶ ማኖ
እና ለሁሉም ተፈታኞች! 🙏
Via የቦንኬ ወረዳ መንግስት
ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት
|| @ASTU_Network
የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ለመውሰድ ወደ አርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ ጉዞ የጀመሩት አቶ ማኖ ማገሶ የዘንድሮውን ፈተና ከምን ጊዜውም በተለየ መልኩ ታሪካዊ አድርገውታል።
የ85 ዓመቱ አባት የካቻ ካሻሶ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪ ሲሆኑ፣ በዚህ ዕድሜያቸው ፈተና መፈተናቸው በእርግጥም ትልቅ አርአያነት ነው።
አቶ ማኖ ማገሶ
* የአምስት ወንዶችና
* የስድስት ሴቶች፣ በድምሩ የአስራ አንድ ልጆች አባት ናቸው።
ቀደም ሲል በጋሞ ጎፋ ክፍለ ሀገር ጋርዱላ አውራጃ የገበሬ ማኅበር ጽ/ቤት ኃላፊ ሆነው ሰርተዋል።
ከዚህም በላይ በገረሴ ወረዳ ጌዣ ደንን በማስተካከል የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርን ከጀመሩት መካከል አንዱ ናቸው።
የካሻሶ ትምህርት ቤትን በማቋቋም እና ለመምህራንና ለአካባቢው ህብረተሰብ ምቹ እንዲሆን ማኖ ገበያን (ወይም ካሻሶ ገበያን) በመክፈት ትልቅ አስተዋጽኦ አድርገዋል።
ልጆቻቸውን በማስተማርም አርባ ምንጭ፣ አዲስ አበባ አልፎ ተርፎም ቻይና ድረስ በትምህርት እንዲደርሱ የረዱ ታላቅ አባት ናቸው።
የቦንኬ ወረዳ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት እንዳስታወቀው፣ የአቶ ማኖ ማገሶ ለ2017 ዓ.ም ሁለተኛ ዙር ማህበራዊ ሳይንስ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተና መፈተን እጅግ ልዩና ታሪካዊ ክስተት ነው።
መልካም ዕድል ለአቶ ማኖ
እና ለሁሉም ተፈታኞች! 🙏
Via የቦንኬ ወረዳ መንግስት
ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት
|| @ASTU_Network
👏8🤣4❤3
ASTU Network ®️
Photo
የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የ2017 ዓ/ም ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል የማህበራዊ ሳይንስ ትምህርት ተፈታኝ ተማሪዎችን እየተቀበለ ይገኛል
==========================
የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የ2017 ዓ/ም የ12 ክፍል ሀገር አቀፍ የማህበራዊ ሳይንስ ትምህርት ተፈታኝ ተማሪዎችን እየተቀበለ ነዉ::
ከሰኔ 23- ሀምሌ 8 /2017 ዓ/ም በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚሰጠዉን የ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲዉ የበላይ አመራሮችና የጸጥታ አካላት አቀባበል እየተደረገላቸዉ ነው:: በዚህ በሁለተኛዉ ዙር የማህበራዊ ሳይንስ 5140 ተማሪዎች በወረቀት እንዲሁም 897 ተማሪዎች ደግሞ በበየነ-መረብ ለፈተናዉ እንደሚቀመጡ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ፕሮግራም ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት ፕሮፌሰር ተገኔ ደሳለኝ ገልፀዋል ።
|| @ASTU_Network
==========================
የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የ2017 ዓ/ም የ12 ክፍል ሀገር አቀፍ የማህበራዊ ሳይንስ ትምህርት ተፈታኝ ተማሪዎችን እየተቀበለ ነዉ::
ከሰኔ 23- ሀምሌ 8 /2017 ዓ/ም በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚሰጠዉን የ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲዉ የበላይ አመራሮችና የጸጥታ አካላት አቀባበል እየተደረገላቸዉ ነው:: በዚህ በሁለተኛዉ ዙር የማህበራዊ ሳይንስ 5140 ተማሪዎች በወረቀት እንዲሁም 897 ተማሪዎች ደግሞ በበየነ-መረብ ለፈተናዉ እንደሚቀመጡ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ፕሮግራም ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት ፕሮፌሰር ተገኔ ደሳለኝ ገልፀዋል ።
|| @ASTU_Network
😢4❤1
የመንግሥት ሠራተኞች "የ5 ሚሊዮን የኢትዮጵያ ኮደርስ ኢንሼቲቭ ነጻ ስልጠና" የግድ ሊወስዱ እንደሆነ ተሰማ።
የበይነ መረብ ስልጠናውን ለመውሰድ ፈቃደኛ ያልሆኑ ሠራተኞች የሥራ እና የደምወዝ እድገት እንዲሁም የዝውውር ዕድል እንደማያገኙ ተሰምቷል።
ስልጠናውን ያጠናቀቀ የመንግሥት ሠራተኛ የምስክር ወረቀቱ ከግል ማህደሩ ጋር እንደሚያያዝ ዋዜማ ምንጮቿን ጠቅሳ ዘግባለች።
የምስክር ወረቀቱን መያዝ እንደ አንድ መስፈት መቀመጡን የጠቀሰው ዘገባው፤ ሁሉም የመንግሥት መዋቅሮች ማሠልጠን ያለባቸውን የሠራተኛ ኮታ እንደተቀመጠላቸው ታውቋል።
አንድ ሠራተኛ ፈተናውን ወስዶ የሚያልፈው ከ20 ከሚያዘው ነጥብ 12 እና ከዚያ በላይ ካመጣ እንደሆነ ተገልጿል።
ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ዓለም አቀፍ ተቀባይነት ያለው ሰርትፍኬት ማግኘት የሚያስችለውን ስልጠና ባለበት ሆኖ መውሰድ ይችላሉ።
ለመመዝገብ 👇
https://www.ethiocoders.et/
የስልጠና ዘርፎች፦
► ዌብ ፕሮግራሚንግ
► አንድሮይድ ማበልፀግ
► ዳታ ሳይንስ
► አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ፋንዳሜንታልስ
©️ tikvahuniversity
|| @ASTU_Network
የበይነ መረብ ስልጠናውን ለመውሰድ ፈቃደኛ ያልሆኑ ሠራተኞች የሥራ እና የደምወዝ እድገት እንዲሁም የዝውውር ዕድል እንደማያገኙ ተሰምቷል።
ስልጠናውን ያጠናቀቀ የመንግሥት ሠራተኛ የምስክር ወረቀቱ ከግል ማህደሩ ጋር እንደሚያያዝ ዋዜማ ምንጮቿን ጠቅሳ ዘግባለች።
የምስክር ወረቀቱን መያዝ እንደ አንድ መስፈት መቀመጡን የጠቀሰው ዘገባው፤ ሁሉም የመንግሥት መዋቅሮች ማሠልጠን ያለባቸውን የሠራተኛ ኮታ እንደተቀመጠላቸው ታውቋል።
አንድ ሠራተኛ ፈተናውን ወስዶ የሚያልፈው ከ20 ከሚያዘው ነጥብ 12 እና ከዚያ በላይ ካመጣ እንደሆነ ተገልጿል።
ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ዓለም አቀፍ ተቀባይነት ያለው ሰርትፍኬት ማግኘት የሚያስችለውን ስልጠና ባለበት ሆኖ መውሰድ ይችላሉ።
ለመመዝገብ 👇
https://www.ethiocoders.et/
የስልጠና ዘርፎች፦
► ዌብ ፕሮግራሚንግ
► አንድሮይድ ማበልፀግ
► ዳታ ሳይንስ
► አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ፋንዳሜንታልስ
©️ tikvahuniversity
|| @ASTU_Network
🤣24❤2
#ዜና
ኢትዮጵያ የራሷን የዋትስአፕ፣ ጂሜይል እና ዙም ስሪቶች እያበለፀገች እንደሆነ መገለጹን፣ ስፑትኒክ ዘገበ።
በኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (ኢንሳ) አማካኝነት የተገነቡት የዲጂታል ቴክኖሎጂ መድረኮች የሳይበር ደህንነትን ለማሻሻል እና ከኢትዮጵያ የቁጥጥር ማዕቀፍ ውጪ በሆኑ የውጭ ኩባንያዎች ላይ ያለውን ጥገኝነት ለመቀነስ የታለሙ መሆናቸውን የሃገር ውስጥ ሚዲያዎችን ጠቅሶ ዘግቧል።
ለጂሜል አማራጭ ሆኖ የቀረበው “እርጋሜል” ከወዲሁ በመንግሥት ተቋማት ሥራ ላይ መዋል እንደጀመረ ተነግሯል፡፡ "ሰርኩትኒ" የዋትስአፕ እና ቴሌግራም ምትክ እንዲሆን የሚጠበቅ ሲሆን ገና በትግብራ ላይ ነው የሚገኘው፡፡
ለቨርቹዋል ግኑኝነቶች እንዲሆን በኢንሳ የበለጸገ የተባለው የዙም ምትክ “ደቦ” ደግሞ የሙከራ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ዘግቧል።
ምንጭ:- Zehabesha
|| @ASTU_Network
ኢትዮጵያ የራሷን የዋትስአፕ፣ ጂሜይል እና ዙም ስሪቶች እያበለፀገች እንደሆነ መገለጹን፣ ስፑትኒክ ዘገበ።
በኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (ኢንሳ) አማካኝነት የተገነቡት የዲጂታል ቴክኖሎጂ መድረኮች የሳይበር ደህንነትን ለማሻሻል እና ከኢትዮጵያ የቁጥጥር ማዕቀፍ ውጪ በሆኑ የውጭ ኩባንያዎች ላይ ያለውን ጥገኝነት ለመቀነስ የታለሙ መሆናቸውን የሃገር ውስጥ ሚዲያዎችን ጠቅሶ ዘግቧል።
ለጂሜል አማራጭ ሆኖ የቀረበው “እርጋሜል” ከወዲሁ በመንግሥት ተቋማት ሥራ ላይ መዋል እንደጀመረ ተነግሯል፡፡ "ሰርኩትኒ" የዋትስአፕ እና ቴሌግራም ምትክ እንዲሆን የሚጠበቅ ሲሆን ገና በትግብራ ላይ ነው የሚገኘው፡፡
ለቨርቹዋል ግኑኝነቶች እንዲሆን በኢንሳ የበለጸገ የተባለው የዙም ምትክ “ደቦ” ደግሞ የሙከራ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ዘግቧል።
ምንጭ:- Zehabesha
|| @ASTU_Network
🤣38❤8🗿2👍1😱1
#Update
The student portal is now reopened. If you have anything to check or edit, please do so before it closes.
🔗 Link 🔗
|| @ASTU_Network
The student portal is now reopened. If you have anything to check or edit, please do so before it closes.
🔗 Link 🔗
https://estudent.astu.edu.et
|| @ASTU_Network
😁11🙏3