ጤና ይስጥልኝ ውድ ወላጆች መደበኛው ምዝገባ የተራዘመው ከነርሰሪ ጀምሮ ላሉት ሁሉም ክፍሎች ሲሆን ኤልኬጂ እና ዩኬጂ ላይ አዲስ ለ22 ቱ አዲስ ቅርንጫፍ ማስመዝገብ ለምትፈልጉ ነባር ወላጆች፣ የድርጅቱ ሰራተኞች፣ ባለአክሲዮኖች እና አዲስ ወላጆች ከ28/11/2014 እስከ 01/12/2013 ዓ.ም ቅድመ ምዝገባ ስለሚካሄድ የተማሪውን ውጤት መግልጫ ካርድ ት/ቤት ይዛችሁ በመምጣት ጠዋት ከ3:00 እስከ 6፡30 ከሰዓት ከ7፡30 እስከ 9፡00 ማስመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን
ውድ ወላጆች ለ22 ቱ አዲስ ቅርንጫፍ ት/ቤት ምዝገባ የሚካሄደው አዋሬ አጸደ ሕፃናት መሆኑን እንገልፃለን።
ጤና ይስጥልን ለጀማሪ ተማሪዎች የመደበኛ ምዝገባ ፎርም የሞላችሁ ሰኞ ከ3፡00 እስከ 9፡00 ከቅ/ገብርኤል ሆስፒታል ገባ ብሎ ከአዲሱ የቅድስት አርሴማ እና የቅ/ገብርኤል ቤ/ክርስቲያን ፊት ለፊት በሚገኘው አዲሱ ቅርንጫፍ ት/ቤታችን በመገኘት የመክፈያ ወረቀት ወስዳችሁ ክፍያውን እንድትፈጽሙ በአክብሮት እንገልጻለን።
ዕጣ የምትጠባበቁ ወላጆች ማክሰኞ በ11/12/2013 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡30 ላይ ዕጣ ስለምና ወጣ አዋሬ አጸደ ሕፃናት ት/ቤት ተገኝታችሁ ዕጣ እንድታወጡ እናሳስባለን።
4_5825843126631139786.xlsx
12.7 KB
Share '4_5825843126631139786.xlsx'
ጤና ይስጥልኝ ይህ ለ22 ቅርንጫፍ ት-ቤት ዕጣ የወጣላቸው ተማሪዎች ዝርዝር ነው እስከ ነገ 12/12/2013 ዓ.ም 6፡00 ድረስ ብቻ አዋሬ አጸደ ሕፃናት ት/ቤት ተገኝታችሁ የምዝገባ ፎርም ሞልታችሁ ክፍያ እንድትፈጽሙ እያሳሰብን በተገለጸው ሰዓት ካላስመዘገባችሁ በቦታው ተጠባባቂ ተማሪዎችን የምንጠራ ይሆናል።
እጣ የወጣው ለጀማሪ ተማሪዋች ሲሆን ለኬጂ 2 እና ለኬጂ 3 ተማሪዎች የመግቢያ ፈተና ቀን ሰሞኑን እናሳውቃለን።
ጤና ይስጥልን ለኬጂ 2 እና ለኬጂ 3 ተማሪዎች የመግቢያ ፈተና ነገ 14/12/2013 ዓ.ም 3:00 በአዋሬ አጸደ ህጻናት ፈተና የሚሰጥ መሆኑን እናሳውቃለን።
ዕጣ ተጠባባቂ የነበራችሁ እስከ ነገ 6፡00 መጥታችሁ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን
የተከበራችሁ ወላጆች እንዴት አላችሁ? ጀማሪ ላይ ልጆቻችሁን አስመዝግባችሁ ዕጣ ያልወጣላችሁ ወላጆች ተጠባብቂዎችን ጠርተን ጥቂት ቦታዎች ስለቀሩ በአመዘጋገብ ቅደም ተከተላችሁ መሰረት ስለምናስተናግዳችሁ ሰኞ 17/12/2013 ዓ.ም 4፡00 ሰዓት ላይ አስፈላጊውን ዶክመንት አሟልታችሁ እንድታስመዘግቡ እናሳስባለን።
Forwarded from Esdros S.C
የአክስዮን ማኅበሩ የአቅመ ደካሞችን ቤት ማደስ ጀመረ
************************
ነሐሴ፤18 ቀን 2013 ዓ.ም
ኤስድሮስ ኮንስትራክሽን ንግድና ኢንዱስትሪ አ.ማ በአዲስ ከተማ ወረዳ 7 ውስጥ ከሚገኙ እጅግ በጣም ያረጁ የቀበሌ ቤቶች መካከል በመምረጥ የሙሉ እድሳት ሥራ አስጀምሯል፡፡
ኤስድሮስ ኮንስትራክሽን ንግድና ኢንዱስትሪ አ.ማ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ በኃይሉ ሰለሞን የቤት እድሳቱን ባስጀመሩበት ወቅት ስራው ረጅም ጊዜ እንዳይወስድ ግንባታውን በአጭር ጊዜ በማጠናቀቅ እንደሚያስረክቡ ቃል ገብተዋል፡፡ የቤት እድሳት የሚደረግላቸው ነዋሪ ወ/ሮ አበራሽ ተሰማ በቤቱ ረጅም ዓመታት ሲኖሩ አንድም ጊዜ ታድሶ ስለማያውቅ ወደ መፍረሱ የተቃረበ መሆኑን ገልፀው አሁን ግን የአክስዮን ማኅበሩ ስላደረገላቸው ድገፍ ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡
የአክስዮን ማኅበሩ የበጎ ፍቃድ ሥራዎችን ጊዜና ወቅት ሳይመርጡ በቀጣይ አጠናክረው በማስቀጠል የኅብረተሰቡን ችግር ለመፍታት እንደሚሠራ የኤስድሮስ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ በኃይሉ ሰለሞን ተናግረዋል፡፡
የአክሲዮን ማህበራችንን ድህረ ገፅ https://esdros.com/e/ እና በፌስቡክ ገፃችን https://www.facebook.com/Esdros-Construction-Trade-and-Industry-SC-282021025628947 በመከታተል ወቅታዊ መረጃዎችን ያገኛሉ፡፡
************************
ነሐሴ፤18 ቀን 2013 ዓ.ም
ኤስድሮስ ኮንስትራክሽን ንግድና ኢንዱስትሪ አ.ማ በአዲስ ከተማ ወረዳ 7 ውስጥ ከሚገኙ እጅግ በጣም ያረጁ የቀበሌ ቤቶች መካከል በመምረጥ የሙሉ እድሳት ሥራ አስጀምሯል፡፡
ኤስድሮስ ኮንስትራክሽን ንግድና ኢንዱስትሪ አ.ማ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ በኃይሉ ሰለሞን የቤት እድሳቱን ባስጀመሩበት ወቅት ስራው ረጅም ጊዜ እንዳይወስድ ግንባታውን በአጭር ጊዜ በማጠናቀቅ እንደሚያስረክቡ ቃል ገብተዋል፡፡ የቤት እድሳት የሚደረግላቸው ነዋሪ ወ/ሮ አበራሽ ተሰማ በቤቱ ረጅም ዓመታት ሲኖሩ አንድም ጊዜ ታድሶ ስለማያውቅ ወደ መፍረሱ የተቃረበ መሆኑን ገልፀው አሁን ግን የአክስዮን ማኅበሩ ስላደረገላቸው ድገፍ ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡
የአክስዮን ማኅበሩ የበጎ ፍቃድ ሥራዎችን ጊዜና ወቅት ሳይመርጡ በቀጣይ አጠናክረው በማስቀጠል የኅብረተሰቡን ችግር ለመፍታት እንደሚሠራ የኤስድሮስ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ በኃይሉ ሰለሞን ተናግረዋል፡፡
የአክሲዮን ማህበራችንን ድህረ ገፅ https://esdros.com/e/ እና በፌስቡክ ገፃችን https://www.facebook.com/Esdros-Construction-Trade-and-Industry-SC-282021025628947 በመከታተል ወቅታዊ መረጃዎችን ያገኛሉ፡፡